ቅዳሜ መጋቢት 26/2018 ዓ.ም
አሶሳ፣
የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገ/ኢ/ልማት መምሪያ ሠራተኞቹን ከአዳዲስ አዋጆች እንዲሁም ደንብና መመሪያዎች ጋር የተገናዘቡ እንዲሆን በማሰብ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፍይናንስ ቢሮ ጋር በመተባበር መጋቢት 25/2018 ዓ.ም ለመምሪያው ሰራተኞች ስልጠና ሰጥቷል።
ስልጠናው በዋናነት የተቋሙ ሠራተኞች አዲስ በተሻሻሉ አዋጆች፣ደንቦች እና መመሪያዎች ላይ ጥሩ ግንዛቤ ኖሯቸው በዚሁ አግባብ ተገልጋዮችን እንዲያስተናግዱ ያለመ ነው።
ስልጠናውን የሰጡት ዳይሬክተሮች እና ባለሙያዎች ስልጠና እንዲሰጡ ሲጠየቁ የመጀመሪያቸው እንደሆነ በመግለፅ ሌሎች ተቋማትም የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገ/ኢ/ልማት መምሪያን አርአያ ሊከተሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የመምሪያው ኃላፊ ወ/ሮ ፋጡማ መሀመድ ተቋሙን በአዳዲስ አሰራሮች ለማስተሳሰር የሚያደርጉትን ጥረት ያደነቁት አሰልጣኞቹ ይህንን ጥረታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አደራ ብለዋል።
አሰልጣኞቹ አያይዘውም በየጊዜው አዳዲስ በሚወጡ አዋጆች፣ደንብና መመሪያ ተቋማት ሰራተኞቻቸውን በማሰልጠን በዚሁ አግባብ ባለጉዳዮችን ማስተናገድ እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

